የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት 1 ሺህ 336 ሰዎች ቫይረሱ ሲገኝባቸው 28 ሰዎች ህይወት አልፏል

By Tibebu Kebede

August 19, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 13 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 21 ሺህ 326 የላብራቶሪ ምርመራ 1 ሺህ 336 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በዚህም በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 34 ሺህ 58 መድረሱንም የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ባወጡት መረጃ አመላክተዋል።