ስፓርት

ከ17 ዓመት በታች የሴካፋ ዋንጫ ኢትዮጵያ ከኬንያ የሚያደርጉት ጨዋታ በፋና+

By Yonas Getnet

November 26, 2025

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ዋንጫ (ሴካፋ) ማጣሪያ ውድድር ከምድባቸው ማለፋቸውን ያረጋገጡት ኢትዮጵያ እና ኬንያ ዛሬ 10፡00 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ።

ጠዋታው በፋና+ ቴሌቪዥን ቻናል እና በፋና ዲጂታል አማራጮች በቀጥታ ይተላለፋል።

እኩል 7 ነጥብ በመሰበስብ ለግማሽ ፍጻሜ ማለፋቸውን አረጋግጠው ወደ ሜዳ የሚገቡት ሁለቱ ቡድኖች ምድቡን በበላይነት ለማጠናቀቅ ይፋለማሉ።

በግብ ክፍያ በመብለጥ ምድቡን የሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የመጨረሻውን የምድብ ጨዋታ ቀን 10፡00 ላይ ያከናውናል።

ሰኞ ሕዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው የኬንያ እና የደቡብ ሱዳን ጨዋታ በኬንያ 2 ለ 0 አሸናፊነት መጠናቀቁ የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን አንድ ጨዋታ እየቀረው ለግማሽ ፍጻሜ ማለፉን ማረጋገጡ ይታወሳል።

ከዚህ ጋር በተገናኘ ዛሬ በሚካሄዱ የሴካፋ ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ውድድር ቀን 7፡00 ሰዓት ላይ ደቡብ ሱዳን ከሩዋንዳ ሲገናኙ ቀን 10፡00 ሰዓት ላይ ሱዳን ከብሩንዲ እንዲሁም ምሽት 1፡00 ሰዓት ላይ ኡጋንዳ ከጅቡቲ ይጫወታሉ።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!