ስፓርት

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ኬንያን በማሸነፍ በአንደኝነት ከምድቡ አለፈ

By abel neway

November 26, 2025

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ዋንጫ (ሴካፋ) ማጣሪያ ውድድር የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የኬንያ አቻውን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በዚህም የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ምድቡን በበላይነት በማጠናቀቅ ግማሽ ፍጻሜውን መቀላቀል ችሏል፡፡

ቀን 10 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የኢትዮጵያን ብቸኛ ግብ ዳዊት ካሳው ከመረብ አሳርፏል፡፡