አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 14 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የመጀመሪያና ሁለተኛ ዙር የአንድ ቋት መጠጥ ውሃና ስነ-ንፅህና ብሔራዊ መርሃ ግብር (One Wash National Program) የ2012 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2013 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡
በውይይቱ በአንድ ቋት መጠጥ ውሃና ስነ-ንፅህና መርሃ ግብር በመጀመሪያው ዙር ተጨማሪ ጊዜና በሁለተኛው ዙር የመጀመሪያ ዓመት የተሠሩ ሥራዎች ሪፖርትና የ2013 በጀት ዓመት ዕቅድ በውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡