አዲስ አበባ፣ ሕዳር 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ለኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን 10 ሚሊየን ብር የማበረታቻ ሽልማት አበርክቷል፡፡
ሚኒስቴሩ ብሔራዊ ቡድኑ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉን አስመልክቶ ለቡድኑ የእራት ግብዣ አከናውኗል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ በዚሁ ወቅት እንዳሉት÷ ቡድኑ የመንግሥት እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስራ ውጤት ነው፡፡
ብሔራዊ ቡድኑ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳካ ጊዜ እንደሚያሳልፍም ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ውድድሩን በ3ኛነት በማጠናቀቅ ከ22 ዓመታት በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳታፊ መሆኑን ማረጋገጡ ይታወቃል፡፡
በሰለሞን በቀለ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡- YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Facebook https://web.facebook.com/fanasport Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!