የሀገር ውስጥ ዜና

የፖለቲካ ፓርቲዎች ካለፉ ታሪኮች እና ትርክቶች ቁዘማ ወጥተው ለሀገር ሰላም እና ለህዝቦች አንድነት ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለጸ

By Tibebu Kebede

December 18, 2019

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 8፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) የፖለቲካ ፓርቲዎች ካለፉ ታሪኮች በመማር ለሀገር ሰላም እና ለህዝቦች አንድነት ሊሰሩ እንደሚገባ ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ያነጋገራቸው የታሪክ ምሁራንና ፖለቲከኞች ገለጹ።

በሃረማያ ዩኒቨርሲቲ መምህርና የታሪክ ምሁሩ ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው፥ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያለፉ ታሪኮችንና ትርክቶችን የርዕዮት አለም አካል አድርገዉ መንቀሳቀሳቸውን በማቆም የፖለቲካ ትኩሳት የሚያደርሰዉን አሉታዊ ተጽዕኖ መከላከል እንደሚገባቸው ጠቁመዋል።