የሀገር ውስጥ ዜና

በተለያዩ ዘርፎች በተከናወኑ ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ ነው – አቶ አወል አርባ

By Yonas Getnet

December 13, 2025

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በለተለዩ ዘርፎች በተከናወኑ ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ ነው አሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፡፡

በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ  “የጉባ ብስራቶች ፤ የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች” በሚል መሪ ሃሳብ ሕዝባዊ ውይይት ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ አቶ አወል አርባ፣ የሲዳማ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ በየነ በራሳ እንዲሁም የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ ሀገር የሚገነባው የሕዝብን ተጠቃሚነት በሚያረጋገጥ የለውጥ አስተሳሰብ ነው።

የስንዴ ምርት፣ የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ፣ የአረንጓዴ ዐሻራ እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በተከናወኑ ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት ማስመዘገብ መቻሉን ተናግረዋል፡፡

በሌላ በኩል የከተማ ኮሪደር ልማት የከተሞችን ገጽታ እየቀየረ እንደሚገኝ ነው አጽንኦት የሰጡት፡፡

በጉባ ላይ የታየውን የልማት አንድነት በተለያዩ ዘርፎች ላይ መድገም እንደሚገባ ጠቁመው ÷ ለዚህም ሁሉም በትብብር ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡

ሀዋሳ ከተማ የብልጽግና ተምሳሌትና የተሞክሮ ማዕከል እንድትሆን ይበልጥ መስራት አስፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

አቶ በየነ በራሳ በበኩላቸው÷ ሀዋሳ ከተማን ውብና ምቹ ለማድረግ የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።

ከተማን በአንድ አካል ብቻ መቀየር የማይቻል በመሆኑ በመደመርና ሕዝባዊ ቅንጅትን በማስተባበር ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ጠይቀዋል፡፡

በፍቅርተ ከበደ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast  YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!