የሀገር ውስጥ ዜና

ስምረት ፓርቲ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለመወዳደር ዝግጅት እያደረገ ነው

By Adimasu Aragawu

December 15, 2025

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) ፓርቲ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለመወዳደር ዝግጅት እያደረገ ነው፡፡

በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህጋዊ እውቅና ያገኘው ፓርቲ የምክር ቤቱን የመጀመሪያ ስብሰባ እያካሄደ ይገኛል።

በመድረኩም ፓርቲው ያለፉትን ስድስት ወራት ያከናወናቸውን የስራ አፈጻጸም መገምገምን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያይ የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ አባልና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኃላፊው አቶ ብርሃነ ገ/የሱስ ተናግረዋል።

የ7ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ቅድመ ዝግጅት ከአጀንዳዎች መካከል እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

በዚህም ለምርጫው የሚወዳደሩ ዕጩዎችን ለመምረጥ እና ቅስቀሳ ለማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል።

ምንም እንኳን በትግራይ ክልል የደኅንነት ችግር ቢኖርም ሕዝቡ ይመራኛል የሚለውን አካል በሰላማዊ መንገድ እንዲመርጥ ፓርቲው የበኩሉን ይወጣል ብለዋል።

በነፃነት ፀጋይ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡- YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Facebook https://web.facebook.com/fanasport Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!