የሀገር ውስጥ ዜና

የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቁ ሥራዎችን ሊሰሩ ይገባል – ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ

By Melaku Gedif

December 15, 2025

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቁ ሥራዎች ላይ በትኩረት ሊሰሩ ይገባል አሉ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፡፡

በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው የጥበባት እና ፈጠራ ኢንዱስትሪ የምክክር መድረክ ተጠናቅቋል።

ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ በዚህ ወቅት እንዳሉት ÷ የሕዝቦችን አንድነትና ትስስር እንዲሁም አሰባሳቢ ትርክት ለመገንባት ኪነ ጥበብ ጉልህ ሚና አለው፡፡

የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ትውልድን የመቅረጽ ኃላፊነት እንዳላባቸው ጠቁመው ÷ በተለይም ዜጎችን በሚያቀራርቡ ጉዳዮችና በብሔራዊ ጥቅም ላይ የጥበብን አቅም ማሳየት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል፡፡

ብሔራዊ ጥቅም ከሚረጋገጥባቸው ጉዳዮች መካከል የቀይ ባሕር ጉዳይ አንዱ ነው ያሉት ሚኒስትሯ ÷የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች በጉዳዩ ላይ በትኩረት እንዲሰሩ ጠይቀዋል፡፡

መንግሥት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ገልጸው ÷ለአብነትም መዋቅር ከመዘርጋት ጀምሮ ለጥበብ ምቹ ሁኔታ መፍጠር መቻሉን ጠቁመዋል።

በጀማል አሕመድ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!