የሀገር ውስጥ ዜና

በመዲናዋ የውስጥ ለውስጥ መንገዶችን በሚያጥሩ አካላት ላይ ርምጃ ይወሰዳል

By Abiy Getahun

December 18, 2025

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን የውስጥ ለውስጥ እና አቋራጭ መንገዶችን በሚያጥሩ ነዋሪዎችና ተቋማት ላይ ርምጃ ይወሰዳል አለ።

ባለስልጣኑ በመንገዶች ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታትና የጋራ መፍትሔ ለማስቀመጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሙህዲን ረሻድ (ኢ/ር) እንዳሉት፤ የውስጥ ለውስጥ እና አቋራጭ መንገዶችን ከማጠር እና በበር ከመዝጋት ጋር በተያያዘ ከዚህ በፊት ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።

ነገር ግን አሁንም ድረስ የውስጥ ለውጥ መንገዶችን አጥረው ለግል ጥቅም የሚያውሉ አካላት አሉ ብለዋል፡፡

ከአሁን በኋላ ይህንን ተግባር በሚፈጽሙ አካላት ላይ ተገቢው ርምጃ እንደሚወሰድ ጠቁመው፤ የተገነቡ አጥሮችን የማንሳትና ለዚህ ስራ የወጣውን ወጪ በህግ አግባብ የማስመለስ ሥራ ይሰራል ነው ያሉት።

በባለስልጣኑ የምህንድስና የመንገድ ዘርፍ ከፍተኛ አማካሪ አንዳርጌ ክፈተው በበኩላቸው፤ የውስጥ ለውስጥ መንገዶቹ ዝግ መሆን በዋና መንገዶች ላይ ለሚፈጠር የትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት እንደሚሆን ጠቅሰዋል።

የመንገድ ሀብትን ከህገ ወጥ ድርጊት መከላከልና መጠበቅ የሕብረተሰቡ የጋራ ኃላፊነት ሊሆን እንደሚገባ በውይይቱ ተነስቷል፡፡

በእየሩሳሌም አበበ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡- YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Facebook https://web.facebook.com/fanasport Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!