የሀገር ውስጥ ዜና

ጠ/ሚ ዐቢይ በመስቀል አደባባይ መልሶ ግንባታ ስራ ላይ እየተሳተፉ ላሉ አካላት ምስጋና አቀረቡ

By Feven Bishaw

August 21, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 15፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በመስቀል አደባባይ መልሶ ግንባታ ስራ ላይ እየተሳተፉ ላሉ አካላት ምስጋና አቀረቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስ ቡክ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ፅሁፍ በመስቀል አደባባይ የሚካሄደውን ሥራ በወቅቱ ለማጠናቀቅ ሌት እና ቀን ለሚሠሩ ሁሉ ምስጋናዬ ይድረስ ብለዋል።