ስፓርት

በወርልድ ቴኳንዶ ኢትዮጵያ ተጨማሪ የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች 

By Mikias Ayele

December 19, 2025

‎አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአንጎላ ሉዋንዳ እየተደረገ በሚገኘው 4ኛው የአፍሪካ ወጣቶች ጨዋታ በቴኳንዶ 73 ኪሎ ግራም ዮሐንስ ዘለቀ ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ አምጥቷል።

‎ዮሐንስ በፍፃሜ ጨዋታ ኮትዲቯራዊውን ተጋጣሚ በመርታት ነው የወርቅ ሜዳሊያ ያመጣው።

‎ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮጵያ በ4ኛው የአፍሪካ ወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታ ስምንተኛ የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች፡፡

በሙባረክ ፋንታው