አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታ ዛሬ ቀጥሎ ሲካሄድ ቀን 9 ሰዓት የተገናኙት አንጎላ እና ዚምባቡዌ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።
ጄልሰን ዳላ ለአንጎላ እንዲሁም ኖሌጅ ሙሶና ለዚምባቡዌ ግቦቹን አስቆጥረዋል።
ጨዋታው ቀጥሎ ሲካሄድ ግብጽ እና ደቡብ አፍሪካ ምሽት 12 ሰዓት የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ምሽት 2 ሰዓት ከ30 በምድብ አንድ የሚገኙት ዛምቢያ ከኮሞሮስ እንዲሁም ምሽት 5 ሰዓት አዘጋጇ ሞሮኮ ከማሊ ጋር ይጫወታሉ።