ቢዝነስ

ሲንቄ ኢንቨስትመንት ባንክ ከኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን የስራ ፈቃድ አገኘ

By Yonas Getnet

December 31, 2025

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሲንቄ ኢንቨስትመንት ባንክ በኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ዘርፍ የራሱን ሚና ለመጫወት ፈቃድ ተቀብሎ በይፋ ስራ ጀምሯል።

በስራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የኢንቨስትመንት ባንኩ ስራ አስፈፃሚ ግርማ ሙለታ እንዳሉት፤ ለባንኩ የተሰጠው ፈቃድ ታሪካዊ እና የፈጣን ዕድገቱ ውጤት ነው።

የባንኩን ኢንዱስትሪን ከተቀላቀለ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ የፋይናንስ አፈፃፀም፣ የካፒታል መጠን ዕድገት የተቋማዊ ጥንካሬ እና የአስተዳደር ብቃት በማስመዝገብ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያን መቀላቀል እንደቻለም ነው የተናገሩት።

ሲንቄ ኢንቨስትመንት ባንክ ከ480 ሚሊየን ብር በላይ ኢንቨስት አድርጓል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሐና ተህልቁ በበኩላቸው በዘርፉ ላይ ለመሰማራት ከፍተኛ ፍላጎት መኖሩን ገልጸው፤ የውጭ ተቋማት ጭምር ለመቀላቀል ጥያቄ አቅርበዋል ብለዋል።

በዛሬው ዕለት ስራውን የጀመረው የኢንቨስትመንት ባንኩም የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣንን የተቀላቀለ አምስተኛው ባንክ እንደሆነም ተናግረዋል።

በሰማኸኝ ንጋቱ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!