ስፓርት

ቼልሲ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካን አሰናበተ

By Hailemaryam Tegegn

January 01, 2026

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቼልሲ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካን አሰናብቷል፡፡

የክለቡ ቦርድ በአሰልጣኙ ቆይታ ዙሪያ በዛሬው ዕለት ባደረገው ስብሰባ የጣሊያናዊው አሰልጣኝ ውል እንዲቋረጥ ወስኗል፡፡

እስከ ፈረንጆቹ 2029 በክለቡ የሚያቆይ ውል የነበራቸው ኢንዞ ማሬስካ በስምምነት ከክለቡ ጋር መለያየታቸውን ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡