ቢዝነስ

ልዩ መለያ ኮድ የሌለው ነባሩ የእጅ በእጅ ሽያጭ ደረሰኝ ከነገ ጀምሮ ሥራ ላይ አይውልም – ሚኒስቴሩ

By Yonas Getnet

January 08, 2026

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ልዩ መለያ ኮድ የሌለው ነባሩ የእጅ በእጅ ሽያጭ ደረሰኝ ከነገ ጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሥራ ላይ አይውልም አለ የገቢዎች ሚኒስቴር፡፡

የታክስ ማጭበርበርን ለመከላከል ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) ያለበት የማንዋል ደረሰኝ ከባለፈው ዓመት ታሕሣሥ ወር ጀምሮ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል፡፡

ነባሩ የእጅ በእጅ ሽያጭ ደረሰኝም ከነገ ጀምሮ ሥራ ላይ እንደማይውል ነው ሚኒስቴሩ አጽንኦት የሰጠው፡፡

በዚህ መሰረትም ከነገ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) ያለበት የማንዋል ደረሰኝ ብቻ ለአገልግሎት እንደሚውል ገልጿል፡፡

የሕትመት ጥያቄ አቅርበው የታተመላቸውን ደረሰኝ ያልወሰዱ ግብር ከፋዮች ደግሞ በሚከፍሉበት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ወይም በየታክስ ማዕከላቸው በመገኘት ደረሰኞቻቸውን እንዲረከቡ አሳስቧል።

በተመሳሳይ ግብር ከፋዮች እጃቸው ላይ የሚገኘውን የቀድሞ ደረሰኝ ለየታክስ ማዕከሎቻቸው በመመለስ የመልቀቂያ ሰነድ መውሰድ እንዳለባቸው አመልክቷል፡፡

መመሪያውን በማይተገብሩ አካላት ላይ ሚኒስቴሩ አስፈላጊውን ርምጃ እንደሚወስድም አስገንዝቧል፡፡

በመሳፍንት እያዩ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!