ስፓርት

ፋሲል ከነማ አርባ ምንጭ ከተማን አሸነፈ

By Yonas Getnet

January 25, 2026

አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ17ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ አርባ ምንጭ ከተማን 3 ለ 2 አሸነፈ።

በጨዋታው የፋሲል ከነማን ግቦች ቃልኪዳን ዘላለም (2) እና ናትናኤል ገብረጊዮርጊስ ሲያስቆጥሩ÷ የአርባምንጭ ከተማን ግቦች ታምራት ኢያሱ እና ጸጋየ አበራ (በፍጹም ቅጣት ምት) ከመረብ አገናኝተዋል።

ቀደም ሲል በተደረጉ ጨዋታዎች አዳማ ከተማ እና መቐለ 70 እንደርታ ያለ ምንም ግብ አቻ ሲለያዩ÷ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሀዲያ ሆሳዕናን 2 ለ 1 አሸንፏል።

የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥሎ ሲካሄድ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ባሕር ዳር ከተማ እና ሀዋሳ ከተማ ይገናኛሉ።