ስፓርት

አርባምንጭ ከተማ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን አሸነፈ

By abel neway

February 01, 2026

አዲስ አበባ፣ ጥር 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ18ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርባምንጭ ከተማ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው በዚህ ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ ታምራት እያሱ ባስቆጠራቸው ሁለት ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።

ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን ከሽንፈት ያልታደገውን ብቸኛ ግብ ፍሬው ሰለሞን ከመረብ አሳርፏል፡፡