የሀገር ውስጥ ዜና

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-

By Yonas Getnet

February 03, 2026

👉 ባለፉት ዓመታት ከተከተልነው መንገድ ውስጥ የትምህርት ሥርዓቱን የማሻሻል ስራ አንዱ ነው።

👉 በዚህም የቅድመ መደበኛ ትምህርት ላይ አበክረን ሰርተናል።

👉 ዩኒቨርሲቲን በሚመለከት የነበሩንን ዩኒቨርሲቲዎች በተቻለ መጠን ጥራታቸው ላይ ለመስራት ጥረት አድርገናል።

👉 አሁን ባለው የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዓለም እውቀት ነጻ እና በሁሉም ቤት እኩል የሚደርስ ሆኗል።

👉 ብቃት ማለት የኮሌጅ ዲግሪ ሳይሆን ክህሎት ነው።

👉 የዛሬ መቶ ዓመት በነበረ አይነት አካሄድ ዘመኑን መዋጀት አይቻልም።

👉 እኛ በአጭር ጊዜ ውስጥ የምናስበው ያሉንን ዩኒቨርሲቲዎችን ጥራት ማሻሻል ነው።

👉 ታች ላይ በመስራትና የዲጂታል ክህሎትን በመገንባት ለነገ ውድድር መዘጋጀት ያስፈልጋል።

👉 የመምህራን ስልጠና፣ የመምህራን ኑሮ ማሻሻልና ቴክኖሎጂን መጠቀም ትምህርትን ይቀይራሉ።

👉 መምህራን ማወቅ ያለባቸው ሰው ከስልኩ የሚያገኘውን የዕውቀት ልክ የትኛውም ተቋም አይሰጠውም፥ ስለዚህ የቴክኖሎጂ ክህሎትን ማሳደግ ይገባል።

👉 የጸጥታ ችግር የዛሬን ትምህርት ማስተጓጎል ብቻ ሳይሆን የተማሪዎችን ነገ ጭምር ነው የሚገድለው

👉 ልጆች ትምህርት ቤት እንዳይሄዱ የሚከለክል ነጻ አውጪ ታጋይ ያልተማረ ሰው ሰብስቦ ነገ ምን አይነት መንግስት ይፈጥራል?

👉 ይሄ በጣም አደገኛ ስብራት ነው፥ ይሄንን መግራትና ማስተካከል ያስፈልጋል።

በዮናስ ጌትነት