የሀገር ውስጥ ዜና

 በአጋሮ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት …

By Mikias Ayele

February 06, 2026

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል አጋሮ ከተማ አስተዳደር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ፡፡

ማዕከሉ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ጨምሮ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነው በዛሬው ዕለት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው፡፡

መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት÷ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች የሚገባቸውን አገልግሎት በአንድ ቦታ እንዲያገኙ እያስቻለ ነው።

በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ  ነመራ ቡሊ በበኩላቸው÷ በክልሉ የቅሬታ ምንጭ የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከፍተኛ ሚና አለው ብለዋል።

የኦሮሚያ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ኮከቤ ዲዳ÷ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከዚህ ቀደም ተገልጋዩ ያጋጥመው የነበረውን እንግልት እንደሚያስቀርና አገልግሎት አሰጣጥን እንደሚያቀላጥፍ ተናግረዋል።

በወርቅአፈራሁ ያለው