አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሂሩት ዘመነ በእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ጄኔራል ከሆኑት አምባሳደር እያንት ሽሌይን ጋር ተወያዩ።
ወይዘሮ ሂሩት ዘመነ አምባሳደር እያንት ሽሌይን በትናንትናው እለት በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው መወያየታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።