የሀገር ውስጥ ዜና

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከጋና ፕሬዚዳንት ጆን ማሃማ ጋር ተወያዩ

By Adimasu Aragawu

February 15, 2026

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጋና ፕሬዚዳንት ጆን ማሃማ ጋር ተወያይተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሕበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት÷ በሁለተኛው ቀን የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ጎን ለጎን ፕሬዚዳንት ጆን ማሃማ ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸውን ነው የገለጹት።