አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ ጋር ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት÷ በሁለተኛው ቀን የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ጎን ለጎን ከደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ ጋር መወያየታቸውን አስታውቀዋል።
በዚህም የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸውን አመልክተዋል።