ቢዝነስ

ሦስት አዳዲስ የሀገር ውስጥ አውሮፕላን ማሪፊያዎች በቅርቡ አገልግሎት ይጀምራሉ

By Adimasu Aragawu

February 18, 2026

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሦስት አዳዲስ የሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማሪፊያዎች በሚያዚያ ወር ተመርቀው ስራ ይጀምራሉ አለ የኢትዮጵያ አየር መንገድ።

አየር መንገዱ ባወጣው መረጃ÷ በግንባታ ላይ ከሚገኙት የሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማሪፊያዎች መካከል በመጪው ሚያዚያ ወር ሦስቱን በማስመረቅ በረራ ለመጀመር ማቀዱን አስታውቋል።

እነዚህ አዳዲስ መዳረሻዎች ነገሌ ቦረና፣ ጎሬ መቱ እና ደብረ ማርቆስ መሆናቸውንም አመልክቷል።