ስፓርት

በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

By Yonas Getnet

February 25, 2026

አዲስ አበባ፣ የካቲት 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ወደ 16ቱ ለመግባት አራት የመልስ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ።

በመልስ ጨዋታዎች ቤነፊካን በመጀመሪያው ዙር 1 ለ 0 ያሸነፈው ሪያል ማድሪድ በቤርናቦው ምሽት 5 ሰዓት ላይ የመልሱን ጨዋታ ያደርጋል።

በተመሳሳይ ሰዓት ሞናኮን ከሜዳው ውጪ 3 ለ 2 ያሸነፈው ፒኤስጂ የመልሱን ጨዋታ በሜዳው እና በደጋፊው ፊት ሲያካሂድ፤ በጋላታሳራይ የ5 ለ 2 ሽንፈት የገጠመው ጁቬንቱስ ውጤቱን ለመቀየር በሜዳው ብርቱ ፉክክር ይጠብቀዋል።

ከዚህ ቀደም ብሎ ደግሞ ምሽት 2 ሰዓት ከ45 ላይ በመጀመሪያ ዙር ጨዋታ በዶርትሙንድ የ2 ለ 0 ሽንፈት የገጠመው አታላንታ በሜዳው እና በደጋፊው ፊት ወደ 16 ውስጥ ለመቀላቀል ይጫወታል።

ትናንት ምሽት በተደረጉ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የመልስ ጨዋታዎች 4 ቡድኖች ወደ 16ቱ መቀላቀላቸውን አረጋግጠዋል።

በዚህም ባየር ሊቨርኩሰን ኦሎምፒያኮስን 2 ለ 0፣ ቦዶ ግሊሚት ኢንተር ሚላንን 5 ለ 2፣ ኒውካስል ዩናይትድ ካራባግን 9 ለ 3 እንዲሁም አትሌቲኮ ማድሪድ ክለብ ብሩዥን 7 ለ 4 በሆነ ድምር ውጤት በማሸነፍ ወደ 16ቱ ተቀላቅለዋል።