አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 6ኛው ሀገራዊ የጎዳና ላይ ኢፍጣር መርሐ ግብር በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ መካሄድ ጀምሯል።
የረመዳን ወርን አስመልክቶ “ነጃሺ ለሀገር” በሚል መሪ ሐሳብ በተዘጋጀው የኢፍጣር መርሐ ግብር ላይ ለመሳተፍ በርካታ የእምነቱ ተከታዮች በቦታው ተገኝተዋል።
መርሐ ግብሩ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት እና በኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ትብብር ነው የተዘጋጀው።
በአህመድ አቡዱልባር