አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዶክተር ሜሮን ለገሰ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሕክምና ት/ቤት 3.95 አማካይ ውጤት በማምጣት የከፍተኛ ውጤትና የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ሆናለች፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት በተለያዩ የሕክምና ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 263 አዳዲስ ባለሙያዎችን አስመርቋል፡፡
ዶ/ር ሜሮን ለገሰ ከሕክምና ት/ቤት 3.95 አማካይ ውጤት በማምጣት የከፍተኛ ውጤት እና የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ መሆን ችላለች፡፡
ዶ/ር ሜሮን በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሴት ተማሪዎች ውጤታማነትና ተሳትፎ እየተሻሻለ መምጣቱን ተናግራለች፡፡
በዘርፉ ያገኘችውን እውቀት ለሀገሯና ለወገኖቿ በቅንነት ለማገልገል ዝግጁ እንደሆነች መግለጿንም የዩኒቨርሲቲው መረጃ ያመላክታል፡፡