አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 19 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማእረግ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይ በቦሌ እና በየካ ክፍለ ከተሞች ድንገተኛ ጉብኝት አደረጉ።
ምክትል ከንቲባው በክፍለ ከተሞቹ ተገኝተው የአገልግሎት አሰጣጡን የተመለከቱ ሲሆን ÷በቦሌ ክፍለ ከተማ በነበራቸው ቆይታ በ2012 በጀት አመት የተከናወኑ ተግባራት ተብራርቶላቸዋል።