ስፓርት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን አሸነፈ

By Hailemaryam Tegegn

March 31, 2026

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ቀን 10 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የዋልያዎቹን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ቸርነት ጉግሳ በመጀመሪያው አጋማሽ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በድምር ውጤት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን 4 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮጵያ በ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ድልድል ላይ መካተት ችላለች፡፡