የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያዊው ዶክተር ዮሃንስ በ2019 በሳይንሱ ዓለም አስፈላጊ ከተባሉ 10 ሰዎች ውስጥ አንዱ ሆኑ

By Tibebu Kebede

December 19, 2019

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 9 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊው የሰው ልጅ አመጣጥና የማህበረሰብ ተመራማሪ ዶክተር ዮሃንስ ሀይለሥላሴ በፈረንጆቹ 2019 በሳይንሱ ዓለም አስፈላጊ ከተባሉ 10 ሰዎች ዝርዝር ውስጥ ተካተቱ።

ተመራማሪው በታዋቂው ኔቸር ጋዜጣ ሊጠናቀቅ ቀናት በቀሩት የፈረንጆቹ 2019 በሳይንሱ ዓለም ከ10 ተፈላጊ ሰዎች ዝርዝር ውስጥ ተካተዋል።