ስፓርት

ወላይታ ድቻ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን አሸነፈ

By Yonas Getnet

April 09, 2026

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ መሳይ ሰለሞን ባለቀ ሰዓት ባስቆጠረው ግብ ወላይታ ድቻ ማሸነፍ ችሏል።

ቀደም ብሎ በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ሀድያ ሆሳዕና አርባ ምንጭ ከተማን 1 ለ 0 እንዲሁም ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን 1 ለ 0 ሲያሸንፉ÷ ነገሌ አርሲ እና ኢትዮጵያ መድን 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡