አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የትናንቶችን ባስታወስን ቁጥር የነገዎችን እናፈራለን አሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ÷ዛሬ፣ “እንኳን ለትንሣኤ በዓል አደረሰዎ” ለማለት ወደ ልዑል ራስ መንገሻ ዘንድ ሄደን ነበር ብለዋል።
ልዑል ራስ መንገሻ ታሪክ ዐዋቂ እና ምክር ለጋሽ አንጋፋ አባት መሆናቸውን አውስተዋል፡፡
ሀገራቸውን በቅንነት በየመስኩ ማገልገላቸውን ገልጸው ÷ ዛሬም ንቁና አስታዋሽ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የትናንቶችን ባስታወስን ቁጥር የነገዎችን እናፈራለን ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል።