የሀገር ውስጥ ዜና

በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ ዜጎችን መብትና ክብር በማስጠበቅ በኩል የዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ ውጤት ማሳየት ጀምሯል – የኢትዮጵያ አምባሳደሮች

By Tibebu Kebede

August 26, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 20 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ ዜጎችን መብትና ክብር በማስጠበቅ በኩል የዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲው ጥሩ ጅምር እየታየበት መሆኑን በሳዑዲ ዓረቢያ እና በተባበሩት ዓረብ ኢሚሬትስ የኢትዮጵያ አምባሳደሮች ተናገሩ ።

ችግር ውስጥ የወደቁ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ባሉበት ሀገር የዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ ተግባራዊ መደረጉ ለችግሮቻቸው መፍትሄ ማግኘት እንዲችሉ ማድረጉ ይነገራል።