አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ 33ኛ ሳምንት ጨዋታ ሊቨርፑል እና አስቶን ቪላ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡
በመርሲሳይድ ደርቢ ከኤቨርተን ጋር ጨዋታውን ያደረገው ሊቨርፑል 2 ለ 1 ሲያሸንፍ ሞሀመድ ሳላህ እና ቨርጂል ቫንዳይክ ለሊቨርፑል እንዲሁም ቤቶ ለኤቨርተን ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡
በተመሳሳይ ጨዋታ በቪላ ፓርክ ሰንደርላንድን ያስተናገደው አስቶን ቪላ 4 ለ 3 አሸንፏል፡፡
ኦሌ ዋትኪንስ (ሁለት)፣ ሞርጋን ሮጀርስ እና ታሚ አብርሃም ለአስቶንቪላ እንዲሁም ክሪስ ሪግ፣ ትራይ ሀም እና ዊልሰን ኢስዶር የሰንደርላንድን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡
በሌላ ጨዋታ ኖቲንግሃም ፎረስት ወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኘውን በርንሌይ 4 ለ 1 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል፡፡