የሀገር ውስጥ ዜና

ፕሬዚዳንት ታዬ ከባንግላዲሽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

By Abiy Getahun

April 21, 2026

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከባንግላዲሽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካሊሉር ራህማን (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ታዬ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ በኢትዮጵያ እና ባንግላዲሽ መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት ለማጠናከር ተወያይተናል ብለዋል፡፡

በተጨማሪም በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ እና የሀገራቱን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር ላይ መወያየታቸውን ገልጸዋል፡፡