የሀገር ውስጥ ዜና

ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከስዊዲን አቻቸው ጋር ተወያዩ

By Adimasu Aragawu

April 24, 2026

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞትዎስ (ዶ/ር) ከስዊድን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማሪያ ማልመር ስቴነርጋርድ ጋር ተወያይተዋል።

ሚኒስትሮቹ በስዊድን ስቶኮልም ያደረጉት ውይይት በአፍሪካ ቀንድ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑ ተመላክቷል።

ጌዲዮን (ዶ/ር) ሁለቱ ሀገራት ታሪካዊና ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ግንኙነት እንዳላቸው በማንሳት ወዳጅነቱን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

በንግድና ኢንቨስትመንት ረገድ የበለጠ ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ገልጸው÷ የስዊዲን ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በተፈጠረው ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል።

ማሪያ ማልመር ስቴነርጋርድ በበኩላቸው÷ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት ጠንካራ መሆኑን ጠቁመው÷ ስዊዲን በሁለትዮሽ እና ባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር የበለጠ ማጠናከር እንደምትፈልግ መግለጻቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል።