አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከሸገር ወደ ሀገር በሚል ርእስ የአዲስ ወግ የውይይት መድረክ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ተካሂዷል።
በውይይት መድረኩ ላይም የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የቱሪዝም ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር አብረሃም በላይ፣ የገንዘብ ሚኒስትር ደኤታ ዶክተር ኢዮብ ተካልኝ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ ጨምሮ ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል።