አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ20ኛ ሳምንት ተስተካካይ መርሐ ግብር ዛሬ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና ጨዋታቸውን አድርገዋል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን 3 ለ 1 አሸንፏል፡፡
የኢትዮጵያ ቡናን የማሸነፊያ ግቦች ኦካይ ጁል፣ ቢኒያም ጌታቸውና ዘላለም አባተ ሲያስቆጥሩ÷ የቅዱስ ጊዮርጊስን ብቸኛ ግብ ደግሞ ፍጹም ጥላሁን ከመረብ አሳርፏል፡፡