አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አዲስ በቅንጦት እቃዎች ላይ (ኤክሳይዝ ታክስ) የሚጣለው ቀረጥ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡ ይታወቃል።
ረቂቅ አዋጁ መንግስት ተገቢውን ግብር መሰብሰብ እንዲችል የሚያግዝ፣ ኮንትሮባንድ እና ህገወጥ ንግድን በመከላከል ረገድ አስተዋፅኦ የሚያደርግ እንዲሁም የህብረተሰቡን ጤና በሚጎዱ እና የማህበራዊ ችግር በሚያስከትሉ በተጨማሪም መሰረታዊ በመሆናቸው ምክንያት የገበያ ተፈላጊነታቸው በማይቀንስ እቃዎች እና አገልግሎቶች ላይ ቀረጥ መጣል በማስፈለጉ መዘጋጀቱም ተገልጿል።