አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ የፓን አፍሪካ ፓርላማ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው ተመርጠዋል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት ዶ/ር አሸብር የፓን አፍሪካ ፓርላማ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸውን የምክር ቤቱ መረጃ አመላክቷል።
ምክር ቤቱ በዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ መመረጥ የተሰማውን ደስታ በመግለጽ መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላቸውም ተመኝቷል።