የሀገር ውስጥ ዜና

በሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ንፋስ በቀላቀለ ዝናብ ከ11 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ

By Meseret Demissu

August 27, 2020

አዲስ አበባ፤ ነሀሴ 21 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን አንኮበር ወረዳ ከፍተኛ ንፋስ በቀላቀለ ዝናብ ከ 11 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል።

የአንኮበር ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት የአደጋ መከላከልና ፈጣን ምላሽ ቡድን መሪ አቶ ሰለሞን ሽፈራ÷ አደጋው የተከሰተው ለነሃሴ 20 አጥቢያ መሆኑን ገልጸዋል ።