የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ ክልል የአርሶ አደር መንደርን በግብርና ልማት የማሻሻል ፕሮጀክት ውጤት እያሳየ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ገለፁ

By Tibebu Kebede

August 28, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 22 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) አርሶ አደሮችን በገበያ ተኮር የግብርና ልማት በማሰማራት ኑሯቸውን የተሻለ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ አስታወቁ።

ርዕሰ መስተዳድሩና የክልሉ ምክር ቤት አፈጉባኤ ወይዘሮ ወርቅሰሙ ማሞ በደቡብ ጎንደር ዞን ደራ ወረዳ መንደርን የመቀየር ፕሮጀክት ጎብኝተዋል::