የሀገር ውስጥ ዜና

በመዲናዋ ከፈረንጆቹ 2014 በፊት ተመርተው አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ተሽከርካሪዎች ከፍተኛውን ለጤና ጎጂ የሆኑ ብናኝ ወደ ከባቢ አየር እንደሚለቁ ጥናት አመለከተ

By Tibebu Kebede

August 28, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 22 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ በትራንስፖርቱ ዘርፍ የሚታየውን የብክለት መጠን ምን ያክል እንደሆነ ለማወቅ እንዲረዳ በመሳሪያ የታገዘ መረጃ በመሰብሰብ ጥናት መካሄዱን የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን አስታውቋል።

ኮሚሽኑ ከሲ 40 ከተሞች የአመራሮች ቡድን ለአየር ንብረት ለውጥ እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ጥናቱን አካሂዷል።