አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ በ700 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው ተለዋጭ መንገድ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።
7 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው ተለዋጭ መንገዱ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነው የተመረቀው።
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሙስጠፌ መሐመድ በዚሁ ወቅት እንዳሉት÷ በክልሉ በመሰረተ ልማት ሥራዎች ተጨባጭ ስኬት ተገኝተዋል።
ተለዋጭ መንገዱ ለምስራቁ የሀገሪቱ ክፍል የንግድ እንቅስቃሴ መጎልበት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለውም አንስተዋል።
የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው÷ ተለዋጭ መንገዱ ለጅግጅጋ ከተማ የኢኮኖሚ አቅም፣ ውበትና እድገት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ጠቁመዋል።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚደረጉ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡ ያደርጋልም ብለዋል።
በተስፋዬ ኃይሉ