አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሰላ ምርጫ ክልል ለሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቁሳቁስ የማከፋፈል ስራ ተጀምሯል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፊታችን ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ይታወቃል። በዚህም ለምርጫው አስፈላጊ ዝግጅቶች በየምርጫ ክልሎቹ እየተካሄደ ይገኛል።
በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአሰላ የምርጫ ክልል ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጋላን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት÷ የምርጫ ቁሳቁስ በተገቢው ጥንቃቄ ለምርጫ ጣቢዎች እየተከፋፈለ ነው። በአሰላ ምርጫ ክልል 108 የምርጫ ጣቢያዎች መኖራቸውን ገልጸው÷ ምርጫው ሰላማዊና ፍትሃዊ እንዲሆን የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል። በአብደላ አማን