የሀገር ውስጥ ዜና

የጎርፍ አደጋን ለመቅረፍ በተፋሰስ ልማት ስራዎች ላይ ትኩረት ሊደረግ ይገባል – አቶ ደመቀ መኮንን

By Feven Bishaw

August 28, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 22 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የጎርፍ አደጋን በዘላቂነት ለመቅረፍ በተፋሰስ ልማት ስራዎች ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን አሳሰቡ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጎርፍ በተጎዱ አካባቢዎች ተላላፊ በሽታዎች እንዳይከሰቱ ከወዲሁ ጥንቃቄ እንዲደረግም መመሪያ ሰጥተዋል።