የሀገር ውስጥ ዜና

በቴሌኮም ማጭበርበር ድርጊት የተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

By Feven Bishaw

August 28, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 22 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ)በህገወጥ የቴሌኮም ማጭበርበር ድርጊት የተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች ከነመሳሪያቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የብሄራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ፡፡

የብሄራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ከውጭ አገር ወደ ኢትዮጵያ የሚደረጉ የስልክ ጥሪዎችን በኢትዮ ቴሌኮም ሳተላይት ኔትወርክ በኩል ማለፍ ሲገባቸው ፤ህገወጥ የቴሎኮም መሳሪያዎችን ህጋዊ ፈቃድ ሳይኖራቸው ወደ አገር ውስጥ በማስገባትና ዓለምአቀፍ ጥሪዎችን በመጥለፍ በራሳቸው መሰመሮች ለደንበኞች እያቀረቡ ህገወጥ ድርጊት ሲፈጽሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎች ናቸው በቁጥጥር ሰር የዋሉት፡፡