የሀገር ውስጥ ዜና

1 ሺህ 131 የምርጫ ክልል ውጤቶች ወደ ማረጋገጫ ማዕከል ደረሱ

By Melaku Gedif

June 11, 2026

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ1 ሺህ 139 የምርጫ ክልል ውጤቶች 1 ሺህ 131 ያህሉ ወደ ማረጋገጫ ማዕከል ደርሰዋል አሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ።

ሰብሳቢዋ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት÷ አሁን ላይ ከ501 የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ምርጫ ክልሎች ውስጥ 497ቱ ወደ ማረጋገጫ ማዕከል ደርሰዋል፡፡

እንዲሁም ከ638 የክልል ምክር ቤት ምርጫ ክልሎች 634ቱ ወደ ቦርዱ ማረጋገጫ ማዕከል መድረሳቸውን አስታውቀዋል።

120 የሚሆኑ የምርጫ ክልሎች ላይ ቅሬታ መቅረቡን ጠቅሰው÷ ጉዳዩ በሕግ ባለሙያዎች እየተጣራ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡

148 ምስክሮች በተለያዩ ቅሬታዎች ላይ ምስክርነታቸውን መስጠታቸውንም ነው የገለጹት፡፡

በሶስና አለማየሁ