የሀገር ውስጥ ዜና

ስፔን ሳዑዲ አረቢያን 4 ለ 0 አሸነፈች

By Mikias Ayele

June 21, 2026

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ በምድብ ስምንት የምትገኘው ስፔን ሳዑዲ አረቢያን 4 ለ 0 አሸነፈች፡፡

ዛሬ ምሽት በተደረገው የምድብ 2ኛ ጨዋታ የስፔንን የድል ግቦች ላሚን ያማል፣ ሚኬል ኦያርዛባል (ሁለት) እና ታማባክቲ (በራሱ መረብ ላይ) አስቆጥረዋል፡፡

በዚሁ ምድብ የሚገኙት ዩራጋይ እና ኬፕቨርዴ ሌሊት 7 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በምድብ ሰባት ቤልጂየም ከኢራን ምሽት 4 ሰዓት ላይ እንዲሁም ኒውዚላንድ ከግብጽ ሌሊት 10 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ፡፡