አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም ብልፅግና ፓርቲ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በማሸነፉ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው÷ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ፓርቲያቸው ብልፅግና በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በማሸነፋቸው ልባዊ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቴን አስተላልፋለሁ ብለዋል፡፡
በማሌዥያ መሪዎች ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን ጉብኝት በአዲስ አበባ ማድረጋቸውን አስታውሰው÷ በተደረገላቸው አቀባበል መደሰታቸውን እና ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መወያየታቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በነበረው ውይይት ታዳጊ የደቡብ ሀገራት እኩልነታቸውን እንዲያረጋግጡ በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ ምክክር ማድረጋቸውን ገልፀዋል፡፡
ማሌዥያ ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ለምታደርገው ትብብር ኢትዮጵያ አስፈላጊ መሆኗን ገልጸው÷ ትብብሮችን በማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡